|
ኢየሩሳሌም የእስራኤል ዋና ከተማ ነው። የድሮ ታሪኮች ስለ ሞሉት፣ ብዙ ሰዎች ቱሪስት ሆነው መጥትው ያዩታል።
እስራኤል በ1949 እ.ኤ.አ. ዋና ከተማነቱን ከቴል አቪቭ ወደ ምዕራብ ኢየሩሳሌም አዛወረች። በ1967 እ.ኤ.አ. በተዋጀ ጦርነት ምሥራቅ ኢየሩሳሌምን ደግሞ ያዘች። በ1980 እ.ኤ.አ. እስራኤል ሙሉ ከተማውን ዋና ከተማዋ ሆኖ ሾመችው። ነግር ግን አብዛኛው አገራት ይህን አድራጎት ሳይቀበሉ ኤምባሲዎቻቸው እስካሁን በቴል አቪቭ ናቸው የሚገኙ። ፍልስጤም ደግሞ ዋና ከተማውን አድርጎታልና ዛሬም በጣም ተቃራኒ ጉዳይ ሆኗል።
የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 695,500 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 31°47′ ሰሜን ኬክሮስ እና 35°13′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
-
Questions for article:
|